ኢትዮጵያ ውስጥ ላለው ችግር መልሱ “የበለጠ ነፃነት እንጂ መገደብ አይደለም” ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ የተጣለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አስመልክቶ ሃገራቸው ስትገልፅ የቆየችውን አቋም ያጠናከሩት ቲለርሰን መሰብሰብንና ሃሣብን የመግለፅ ነፃነትን የመሳሰሉትን መብቶች እንደሚገድብ አመልክተው አዋጁ በተቻለ ፍጥነት እንዲነሣ ጠይቀዋል። ኢትዮጵያዊያን ዜጎችም ሃሣባቸውን በሰላማዊ መንገድ ብቻ የመግለፅ ኃላፊነት እንዳለባቸው ቲለርሰን አሳስበዋል።
ሙሉውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያገኛሉ።
Related stories The National Movement of Amhara(NaMA) Denounces International Violations of the Sovereignty of Ethiopia
Powered by Inline Related Posts