በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ መንጋገርን፣ መደራደርን፣ ሽምግልናን የሚያወግዙ ” ኢትዮጵያዊያን” መኖራቸው ያስደነግጣል። የትኛዋን አገር ለመጥቀም እንደሚሰሩም ለመረዳት ያስቸግራል። በኢትዮጵያ እርቅና ሰላም ቢወርድ ለምን እንደሚከፋቸው መገመትም ያዳግታል። ዛሬ ከየጥጉ የሚወረወረው ይህ አይነቱ አባዜ ወዴት እንደሚወስደን አለመረዳት የእውቀት ማነስ ሳይሆን ” የኪሴን ልሙላ” አባዜና በንዋይ እሳቤ የመቀንዘር ለባዊ ሴሰኛነት ነው።
ፎቶ – የተፈናቀሉ ወገኖች ናቸው። አሁን የሚፈለገውም ከሰላም ይልቅ ህዝብ እንዲያልቅና እንዲፈናቀል በመሆኑ የርቅ ሃሳብ የተወገዘ ነው
የኢትዮጵያ የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የአገር ሽማግሌዎች ጥምረት የፌድራል መንግሥት እና በትግራይ መካከል የተካረረውን ልዩነት ለማስታረቅ ወደ መቐለ ያመሩት የትግራይ ክልል ባለስልጣናት ፈቃዳቸውን በማሳየታቸው እንደሆነ ለጀርመን ራዲዮ አረጋግጠዋል። ይሁን እንጂ ከመንግስት ወገን ምን ዓይነት ምላሽ እንደተሰጣቸው ያሉት ነገር የለም።
የኢትዮጵያ የየሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ሐጂ መስዑድ አደም የኢትዮጵያ ነባራዊ ፖለቲካ የሐይማኖት መሪዎች እና የአገር ሽማግሌዎችን “ጣልቃ ገብነት ይፈልጋል” ሲሉ ለዶይቼ ቬለ ሲያስታወቁ ፣ ለሽምግልናው ይሁንታ የሰጡት የትግራይ ክልል ከፍተኛ አመራሮች የሐይማኖት ተቋማት መሪዎች እና የአገር ሽማግሌዎች በሚያደርጉት ጥረት የተሳካ ውጤት እንደሚያመጡ እመነታቸውንም ገልጸዋል።
አቶ ታዬ በፊስቡካቸው የጻፉት