በኢትዮጵያ የሚገኙ ንግድ ባንኮች ከሚያቀርቡት ብድር 5 በመቶውን በተንቀሳቃሽ ንብረት ለሚሰጥ የብድር አይነት እንዲያውሉት የሚያዝ መመሪያ ማውጣቱን ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ተንቀሳቃሽ ንብቶሮችን በዋስትና አስይዞ መበደር የሚያስችለው መመሪያ ላይ ከፋይናንስ ተቋማት ተወካዮች ጋር ውይይት አካሂዷል።
ብሄራዊ ባንኩ ከዚህ በተጨማሪም ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች አስይዘው የሚበደሯቸውን ንብረቶች የኢንሹራንስ ተጠቃሚ በሚያደርገው የማይክሮ ኢንሹራን መመሪያ ላይም ከፋይናንስ ተቋማት ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።
ከዚህ ቀደም ቋሚ የሆኑ ንብረቶችን ብቻ በማስያዝ ይደረግ የነበረውን የብድር ስርአት ይቀይራል የተባለለት መመሪያው በዋናነት አርሶ አደሩን ፤አርብቶ አደሩን ፤የፈጠራ ባለሙያዎችን እና ሌሎች ተንቀሳቃሽ ንብረቶችን አስይዘው መበደር የሚችሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የብሄራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ገልጸዋል።
የብድር ስርአቱ በሀገሪቱ የሚገኙ በተለይም በግብርናው ዘርፍ ያሉ ሀብቶችን አሟጦ ለመጠቀም እንደሚያግዝ የተናገሩት ብሄራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ኢንቨስትመንትን በማበረታታት እና የስራ እድልን በመፍጠርም ጉልህ ድርሻ ያበረክታል ነው ያሉት።
ከዚህ ባለፈም መመሪያው አሁን ላይ በሀገሪቱ በሁሉም ዘርፎች ያለውን የተበዳሪዎች ቁጥር ከ260 ሺህ በላይ እንደሚያሳድግ እና ለፋይናንስ ዘርፉ አዲስ መንገድን ከፋች መመሪያ መሆኑን ዶክተር ይናገር ደሴ ተናግረዋል።
ዶክተር ይናገር ደሴ መመሪያ ባንኮች በዓመት ለተለያዩ ዘርፎች ለብድር ከሚያቀርቡት ገንዘብ ውስጥ 5 ከመቶ የሚሆነውን ለተንቀሳቃሽ ንብረት ለሚያቀርቡ ተበዳሪዎች ማዘጋጀት እንዳለባቸው መመሪያው እንደሚያዝ ገልጸዋል።
የብሄራዊ ባንክ በቀጣይ ዓመት መመሪያው ተግባራዊ እንዲደረግ የተለያዩ ዝግጅቶችን እያደረገ መሆኑን የገለጹት ገዥው ተንቀሳቃሽ ንብረቶችን አስይዘው መበደር የሚፈልጉ ዜጎችን ለመመዝገብ በማእከል ደረጃ የመመዝገቢያ ስርዓት መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ተንቀሳቃሽ ንብረቶችን አስይዞ መበደርን የሚፈቅደው አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት በዘንድሮ ዓመት መጽደቁ ይታወሳል።
በጥበበስላሴ ጀምበሩ
(ኤፍ.ቢ.ሲ)
- “ፍትህ ለትግራይ! ሞት ለመከላከያ ሰራዊትና … በትግራይ ሕዝብ ስም ትህነግ የመዘዙ ምንጭ ላይሆን?ድሮ ገና በፊት የወደፊቱ የታያቸው ” በስሜ አታድርጉት በሉዋቸው” ሲሉ እያለቀሱ ለምነዋል። ጀርመኖች አይሁዶችን ሲጨፈጭፉ ነበር የወደፊቱ የታያቸው ጀርመኖች ” do not do it byContinue Reading
- የአምነስቲ ” ሽንቁረ ብዙ” ሪፖርት የተከፋዮች የቲውተር ዜና ድምርአገር መከላከያ ባላሳበው መንገድ ተጨፍጭፏል። በመኪና ተጨፍልቋል። እንደጠላት ” ሌባ ” እየተባ ባዶ እግሩን መሳሪያ ተወድሮበት ተተፍቶበታል፤ ብወልቃይት ጠገዴ፣ በራያ የሚኖሩ ሰዎች ላይ የተፈጸመው ግፍ፣Continue Reading
- Ministry Urges Amnesty Int’l to Use Appropriate Sources in Report to Uncover the TruthAmnesty International should use appropriate sources in its report to uncover the truth regarding allegations related to the incidents in the city of Axum, accordingContinue Reading
- Ethiopia: Eritrean troops’ massacre of hundreds of Axum civilians may amount to crime against humanityAmnesty International interviewed 41 survivors and witnesses to mass killings in November Troops carried out extrajudicial executions, indiscriminate shelling and widespread looting Satellite imagery analysisContinue Reading