ቀደም ባሉት ዓመታት መጠኑ ይህን ያህል ባይሆንም ከሰበታ አንድ የመሬት ምሪት ሃላፊ መሐንዲስ መኖሪያ ቤት ሮቶ የውሃ ጋን ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው ብር ተይዞ ነበር። ከዚያ ግዜ በሁዋላ ገንዘብ አልጋ ስር ተቀብሮ ሲገኝ በብዛትም በዓይነትም ይህ ትልቁ ነው።
ባሌስትራ ወርቅ ነው በማለት በቅንጅት ብሄራዊ ባንክን ሲዘርፉ የነበሩ ከበርካታ ጩኸት በሁዋላ ዋናዎቹ ጠግበው ከኮበለሉ በሁዋላ በቁጥጥር ስር የዋሉት ዱርዬ ሃብታሞች ቤት ሲፈተሽ ብር የተገኘው እመኝታ ስር በተሰራ የአርማታ ጉድጓድ ውስጥ ነበር። አንደኛው ተጠርጣሪ በአርማታ እተሰራው ጉድጓድ ላይ ዘመናዊ ማድራስ አድርጎ ለእናቱ ከላይ ያስተኛ ነበር። ይህ ዜና በውቅቱ አስገራሚ ነበር።
ዛሬ ከሰበታ የተሰማው ሌላ ዜና ደግሞ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ብሮች አልጋ ስር ተከማሽቶ መገነቱ ነው። የተገኘው ደግሞ አንድ ፓኪስታናዊ ተከራይቶ በሚኖርበት የመኖሪያ ቤት ውስጥ ነው። ፋና የከተማውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቀነኒሳ ዳዲ ጠቅሶ እንደዘገበው ከ3 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር በላይ የእገር ውስጥ ብርና የውጭ ሀገራት ገንዘቦች በተጠቀሰው ሰው ቤት ተከማችቶ ተይዟል።
ከተማው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቀነኒሳ ዳዲ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት የተያዘው ገንዘብ 3 ሚሊየን 751 ሺህ 830 የኢትዮጵያ ብር፣ 2 ሺህ 950 የአሜሪካ ዶላር እና የዱባይ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬት፣ የፓኪስታንና የኦማን ገንዘቦች ናቸው፡፡
በከተማው የ3ኛ ክፍለ ከተማ የፖሊስ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ታደሰ ሁሪሳ ገንዘቡ በግለሰብ ቤት ውስጥ አልጋ ስር ተከማችቶ የተያዘው በህብረተሰቡ ጥቆማና በፀጥታ መዋቅር ክትትል ነው ብለዋል፡፡ገንዘቡ የተያዘው አንድ ፓኪስታናዊ ተከራይቶ በሚኖርበት የመኖሪያ ቤት ውስጥ ነውም ብለዋል ኃላፊው፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ወደ ፊትም ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርና ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን ለመቆጣጠር በትኩረት የሚሰራ መሆኑን አቶ ቀነኒሳ ዳዲ ተናግረዋል፡፡
- አትሌት ለተሰንበት ግደይ በቶክዮ ኦሎምፒክ ትሳተፉለች!!“በትግራይ ክልል በነበረው ግጭት የአትሌቷ ልምምድ ተስተጓጉሎ ይሆን?” የሚል ጥያቄ ከኢትዮጵያ ቼክ የቀረበለት አልጣኝ ሀይሌ “በነበረው ችግር ምክንያት አርፍደን መጥተናል። እኛ የነበርነው ደቡባዊ ትግራይ አካባቢContinue Reading
- የእናት አገር ጥሪ አዋጅ ታወጀ –የዱባይ ጸሃይ እንዳትሞቅ ተለክታ በመስፈሪያ ቤቱ ትፈሳለች። ባህር ላይ ተንጣሎ የሰፈረው ቤት የአረብ ንጉሳዊያን መኖሪያ መቅደስ እንጂ የአንድ ለማኝ አገር ዜጋ አይመስልም። ለጊዜው ፓላስ እንበለው።Continue Reading
- CDC Group Targets $1 Billion of African Investments in 2021Centers for disease control and prevention (CDC) Group is planning about $1 billion in Africa investments this year in sectors including infrastructure and finance andContinue Reading
- አብይ አሕመድና ጣጣቴዎች – “አብይ አሕመድ ባይታመሙ ነበር የሚገርመው”“አብይ አህመድ ሰው ናቸው። አብይ አህመድ ሰው ላይ ሊደርስ የሚችለው ሁሉ ይደርስባቸዋል። በመሆኑም ቢታመሙ፣ ጉዳት ቢደርስባቸው አይገርምም። ላለፉት ሶሰት ዓመታት ጉያቸው ውስጥ በተሰገሰጉ እንግዴ ልጆችContinue Reading