የፌዴራል ፖሊስ ጥብቅ ፍተሻ እያደረገ ያለው ከአማራ ክልል በሚመጡ መንገደኞች ብቻ ሳይሆን ወደ መዲናዋ በሚያስገቡ በሁሉም በሮች ላይ ተመሳሳይ የቁጥጥር ስራ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው ጣሰው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በአልን ምክኒያት በማድረግ በአዲስ አበባ የሽብር ድርጊት ለመፈጸም እና ይህንኑ ተከትሎ ሁከት እና ግጭት እንዲፈጠር በዝግጅት ላይ የሚገኙ አካላት እንዳሉ ደርሰንበታል ያሉት ኮሚሽነር ጄኔራሉ መረጃውን መሰረት በማድረግ ወደ አዲስ አበባ በሚያስገቡ በሁሉም በሮች ላይ ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።
የበዓሉን እንቅስቃሴ ለማደፍረስ ዕቅድ ያላቸው ሀይሎች እንዳሉ ፖሊስ በምርመራ እንደደረሰበት ጠቁመው፤ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቀቆጠቡ አሳስበዋል።
ከመስከረም 25 በኋላ መንግስት አይኖርም በሚል የተለያዩ እንስቃሴዎች የሚያደርጉ አካላት እንዳሉ ገልጸው የህዝቡን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል።
በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ወደ አዲስ አበባ መግቢያ በሮች በሱልልታ፣ ለገጣፎ፣ ቡራዩ፣ ገላንና ሰበታ ፍተሻ እየተደረገ እንደሆነም ኮሚሽነር እንዳሻው ጣሰው ተናግረዋል።
አላስፈላጊ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት ፖሊስ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን ገልጸው፤ በበዓሉ ለመታደም የሚመጡ ምዕምናንና እንግዶችም ትክክልኛውን የይለፍ ባጅ ማድርጋቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው ተናግረዋል። ይህን ተላልፎ በሚገኝ ማንኛውንም አካል አይታገስም ፤ ፖሊስ እርምጃ ይወስዳልም ብለዋል።
ፖሊስ ከኅብረተሰብ ጋር በትብብር እየሰራ ነው ያሉት ሀላፊው፤ ህብረተሰቡ ለየት ያለ እንቅስቃሴ ሲመለከት የተለመደ ትብብርንና ጥቆማውን ለፖሊስ እንዲሰጥ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
- First Russian warship enters Port Sudan ahead of plans to open naval base: InterfaxThe Russian warship, “Admiral Grigorovich” frigate, entered the Sudanese port where Moscow plans to build a naval base on the country’s Red Sea coast, Russia’s Interfax newsContinue Reading
- US Attempt To Make Pronouncements On Ethiopia’s Internal Affairs Regrettable :MoFAThe Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia (MoFA) has rejected the press statement issued by the US Secretary of State Mr. Antony J. Blinken yesterdayContinue Reading
- “አማራ ከትግራይ ክልል ውጣ”አሜሪካ ”ግፍ” ታውቃለች? ጋምቤላ፣ ማይካድራ፣ ራያ፣ በደኖ፣ሆራ፣ ዋተር…ምን ተደርጓል?አሜሪካ እጅግ አስገራሚ መግለጫ አሰራጭታለች። አማራ ከትግራይ ክልል ይውጣ ብላለች። በትግራይ ግፍ መፈጸሙን አምናለች። ግን ለሜሪካ ” ግፍ” ምንድን ነው? አሜሪካኖች ስለ ግፍ የማውራት ሞራልContinue Reading
- WAR, JUSTIFIABLE WAR? “ጦርነት ለሃገር ህልውና” by Dr. Haymanot“አንድ መንግስት ዜጎቹን የመጠበቅ ግዴታ አለበት። በመሆኑም ራስን የመከላከል ጦርነቶች ሁሉ በሥነ ምግባር የተፈቀዱ ናቸው ” የቅዱስ አውጉስቲን አባባል አስቅቀድመው የሜሪካን መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርContinue Reading