ዛሬ የኔታ ማለፋቸውን ሰማን። የዘመኑንን በሽታ ” አድር ባይነትን” አብዝተው በተግባር ሲያኮስሱ የኖሩት መስፋን ለተፈጥሮ መርህ ሲባል ” አለፉ” ይባል እንጂ አሉ። እስኪወሰዱ ብዕራቸው ያልዶለዶመ፣ አረጀሁ፣ ደከምኩ፣ ታመምኩ ብለው እጅ ሳይሰጡ ሃሳብ ሲዘሩ የኖሩ፣ ከሁለት ሳምንት በፌት መጣፍ ያሳተሙ የአገር ምሶሶ እንዴት ሞቱ ይባላል?
በመጥሃፍ አጥገበው፣ የሰው ልጅን ቀርጠው፣ እውነት መናገርን አስተምረው፣ ስደትን ረግመው፣ በተፈጠሩበት ምድር ግናባራቸውን ሰጥተው፣ እስኪሄዱ ባትለው የኖሩ ብሩህ ሰው የኔታ !! እረፍትዎን ሰምቶ የትኛው ልጅዎ ይነሳ ይሆን? ማን አድርባይነትን ፈንቅሎ ይወጣ ይሆን? ዘርዎ ፍሬዋን ታፍራ፤ ባስቀመጡልን ሁሉ ልጅ ልጆቻችን ያስቡዎታል።
የኔታ ከዛሬ ሁለት ሳምንት በፊት አዲስ መጣፍ አሳትመዋል። በ91 ዓመት እድሜ ይህን ያደረገ ማን ነው? አብሪው ኮከብ አልሞትክም፤ አለህ፤ ትኖራለህ፤ ትዘከራለህ፤ ምክንያቱም ህያው ስራህ ምስክር ነዋ! ስለ የኔታ የተለያዩ አስተያየቶች እየጎረፉ ነው
ኢትዮጵያዊነት ከጎሰኝነት በላይና ውጭ የሆነ አጠቃላይ ማንነት ነው :: ኢትዮጵያዊነት የደጋው ብርድና የቆላው ሙቀት የሚገናኙበት የደጋው ዝናብ ከቆላው ወንዝ ጋር የተዛመደበት ሃይል ነው :: ኢትዮጵያዊነት ለሙሴ* ለክርስቶስና ለመሀመድ የሚጨሰው እጣን በእርገት መጥቆ የሚደባለቅበት እምነት ነው :: ኢትዮጵያዊነት በቄጤማ ጉዝጏዝ ላይ የሚታየው መተሳሰብና መፈቃቀር ነው :: ኢትዮጵያዊነት የአስተዋይነት ፣ የሚዛናዊነትና የጨዋነት ባህርይ ነው ~ ረጅምና ተጽፎ ያላለቀም ታሪክ ነው ” የወርቃማ ሀሳቦች ባለቤት የሆኑትን ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም ነፍስ ይማር ! ከተናገሩት ብሎ ዓለማየሁ ገብየሁ ከከተበው
መስከረም 20፤ 2013 ዓም የትውልድ ዋርካ፤ የዘመናት ዕንቁ የሆኑትን የኔታ መስፍን ወልደ ማርያም ማረፋቸው ተሰምቷል። ስለ እርሳቸው ብዙ ማለት ይቻላል። ሞት ለማንም የማይቀር ቢሆንም ስለ እርሳቸው ዕረፍት እኛ ከምንናገረው በላይ ራሳቸው ስለ ሞት የተናገሩትን አትመነዋል። ከሁሉ በላይ “ዛሬም እንደ ትናንት” የተሰኘውን የመጨረሻ መጽሐፋቸውን ከሁለት ሳምንታት በፊት አሳትመው ማረፋቸው ለአገራቸው እስከመጨረሻው የተጉ የዘመናችን ዕንቁ! የኔታ መስፍን! የቅኔ ጌታ! የዕውቀት ገበታ! ቢባልላቸው በፍጹም የሚያንስባቸው አይደለም። ጎልጉል የድረገ ገጽ ጋዜጣ
- Israeli ‘sex tourism’ is the fruit of normalisation with the UAEIt is hard to believe the testimonies of Israeli tourists returning from the UAE, in which they describe Dubai as the Las Vegas of theContinue Reading
- UAE diplomatic delegation intervenes to reactivate Renaissance Dam negotiationsThe official Sudan News Agency (SUNA) announced on Wednesday that a delegation from the United Arab Emirates (UAE) Ministry of Foreign Affairs concluded a one-day visitContinue Reading
- Egypt invetors in Ethiopia request compensation for losses due to Tigray conflictBy Shaimaa Al-Aees Egyptian investors in Ethiopia’s Tigray region are awaiting the federal government’s response to the former’s requests of compensations for production halt and lossesContinue Reading
- “ትህነግ መጀመሪያ ቃል ነበር – ማሌሊትን ለብሶ በእኛ አደረ “እስኪ መለስ ይቀስቀሱ። እስኪ መለስ ፊት ብዙ የድምጽ መቅጃ ይደርደር። ድምጸ ወያኔ ይጠይቅ። ሁሉም ባይሰማ የትግራይ ሕዝብ፣ ከትግራይ ሕዝብም በተለይም ” አምላክ ትግራይን ፈጠረ፣ ትግራይምContinue Reading