“የጁንታው ፀሐይ እየጠለቀች ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ የህግ ማስከበሩ ዘመቻ ወደ መገባደጃው መቃረቡን አስታወቁ። የትግራይ ሕዝብ በጁንታው ቡድን መከራ እያየና ሲያይ የኖረ ሕዝብ እንደሆነም ጠቅሰዋል።
“ይሄንን መርዶ ጁንታው በቁሙ ተረድቶታል” በማለት ጁንታው ቡድን ጸሃይ እንደጠለቀበት የተረዳበትን አግባብ በቲውተር ገጻቸው ያስታወቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ጁንታው ” አሁን የሚይዘውን የሚጨብጠውን የሚያጣበት ጊዜ ነው። በጣዕር መንፈስ በየቦታው የመጨረሻውን የጥፋት ድግስ ይደግስ ይሆናል” ብለዋል።

ሱሉሱ የዞረበት የደደቢቱ ሽፍታ ሲመሽ በርካታ የተስፋ መቁረጥ አስከፊ ወንጀሎችን ሊያከናውን ስለሚችል አብይ አህመድ “ሕዝቡ በንቃትና በተደራጀ መንገድ አካባቢውን እንዲጠብቅ አደራ እላለሁ” የሚል ጥሪ አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ከማለታቸው ቀድሞ ሕዝብ በያለበት ራሱን አደራጅቶ አካባቢውን እየተበቀ እንደሆነ፣ በአዲስ አበባ ብቻ አንድ ቀን ውስጥ ከሁለት ሺህ በላይ የጥቆማ መልዕክት መስጠቱን፣ ከዚህም ውስጥ ከዘጠና በመቶ በላይ ትክክለኛ ጥቆማ መሆኑንን አዳነች አቤቤ ከቀን በፊት ከምስጋና ጋር ማስታወቃቸው ይታወሳል።
ጀንበር ከመጥለቋ ጋር በተያያዘ “የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወገኖቻችን በየአካባቢያችን ምንም ዓይነት አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይደርስባቸው ሁላችንም የወንድሞቻችን ጠባቂ እንሁን” የሚል ጥሪ ያስተላለፉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፣ ” የኢትዮጵያ ጠላት ስግብግቡ ጁንታ ነው። የትግራይ ሕዝብ እንደሌላው ሕዝብ በጁንታው መከራ ያየ ሕዝብ ነው። ጁንታው ለፍርድ እንዲቀርብ የትግራይም ሕዝብ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር አብሮ እየተዋጋ ነው። አካባቢዬን እጠብቃለሁ፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ የመከራ ቀንበር እሰብራለሁ። ጁንታውን ለፍርድ አቀርባለሁ – ይህ ነው ቃል ኪዳናችን” ብለዋል።
በተለያዩ ግንባሮች የተገኘውን ድል ተከትሎ የዘመቻው መሪዎች እንዳስረዱት የትግራይ ሰላማዊው ሕዝብ ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ሰጥቷል። አብሮ ተዋግቷል። መከላከያ በተቆጣጠራቸው ከተሞች ሕዝቡ ከትግራይ ወገኖቹ ጋር ተጋብቶ በፍቅር እንደሚኖርና ችግሩ ያለው ከጁንታውና አረመኔው የህወሃት መሪኦውችና ጋሻጃግሬዎች ጋር ብቻ መሆኑንን ሲናገሩ ተሰምቷል።
- በኢትዮጵያ የትግራይ ጉዳይ ላይ የጸጥታው ምክር ቤት ሳይስማማ ተበተነ፤ አማራ ትህነግን በህግ ሊጠይቅ ነውየተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ስለትግራይ ቢወያይም ያለስምምነት መጠናቀቁን ዲፕሎማቶች እንደነገሩት ጠቅሶ ኤፒ በሰበር ዜናው አመለከተ። ከቀን በፊት ስብሰባው እንደሚካሄድ ውስጥ አዋቂዎች እንደነገሩትContinue Reading
- “ወያኔ እየሠራው ባለው ግፍና በደል ትግራይ ከፍላ የማትጨርሰው ዕዳ እየተቆለለባት ነው!”ሲሉ ሰምቼ…የሌባ ተቀባይ ኃጢኣት ከሌባው ኃጢኣት ቢበልጥ እንጂ አያነስም (ይድረስ ለነአብርሃ ደብረጽዮን ደስታ ገ/ሚካኤል) አምባቸው ደጀኔ (ከወልዲያ – martyrof2011@gmail.com)አብርሃ ደስታን ለመግለጽ ቃላት አጥቼ ብዙ ተቸገርኩ፡፡ ልፍጠርContinue Reading
- PM Abiy, U.S Senator Inhofe Hold Encouraging Conversation about Tigray(ENA) Prime Minister Abiy Ahmed on Wednesday held encouraging conversation with United States Senator Jim Inhofe on the current situation in the Tigray Regional State.Continue Reading
- Let’s See the Proof of “Ethnic Cleansing” in Ethiopia, New York Times!On Sunday, February 28, 2021, I sent an op-ed submission to the editor of the New York Times in response to the article Ethiopia’s War LeadsContinue Reading
- The National Movement of Amhara(NaMA) Denounces International Violations of the Sovereignty of Ethiopia1. Background The National Movement of Amhara(NaMA) Denounces International Violations of the Sovereignty of Ethiopia1. BackgroundDuring the past three decades, Ethiopia went through a grievousContinue Reading