በአካባቢው ሰፍሮ የነበረው የመከላከያ ሃይል በተነደፈለት እቅድ መሰረት እንዴት ተናቦ እንደሚያጠቃ ልምምድ ሲስያደርግ ቆይቶ አካባቢውን ነጻ ለማውጣት ትዕዛዝ ሲጠባበቅ ነበር። በቴሌቪዥን መግለጫ የሰጡት አዋዲዎችና የካርታ ጠቋሚ ” ሞራላችንና እልሃችን ከልክ በላይ ነው። ይህን ጁንታ እንደመሠዋለን። የምንጠብቀው ት ዕዛዝ ብቻ ነው” በማለት ተናግረው ነበር።
እንዳሉት ተግባሩ አልቆየም። መመሪያው እንደተላለፈ ዋጋ ከፍለው፣ በአየር ሃይል ድጋፍ ሰጪነት፣ በከባድ መሳሪያ አጃቢነት ጥቂት መስዋዕትነት በመክፈል ራያንና አካባቢውን ነጻ አውጥተዋል።
የጁንታው አፈ ቀላጤ ” የሮኬት ጥቃቱ ይቀጥላል” በማለት ትንታኔ ሲሰጡ ” ከጥቃቱ በሁዋላ አሁን ውጊያው ጋብ ብሏል” ብለው ነበር። እንዲሁም ” ወደ ማጥቃት እንዛወራለን” ሲሉ ተደምጠው ነበር።
እሳቸው ይህን ባሉ ሰዓታት ውስጥ የመከላከያ ሰራዊትና የአማራ ልዩ ሃይል፣ እንዲሁም ደጀኑ ህዝብ በሚያደርገው ደጋፍ የሚታገዘው የህግ ማስከበር ዘመቻ ለወራት የተማሰውን ምሽግ ተረማምደውበታል። ዛጎል እንደሰማችው ጁንታው ያሰለፋቸው ሃይሎች ክፉኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ተደምሰሰዋል።
” እጅግ ያሳዝናል” ሲሉ ምስክሩ እንደነገሩን እግር አውጪኝ ብሎ የሚሸሸው ሃይል በጁንታው ሃይል ” እለምን ትሸሻለህ” በሚል ቅጣት ተቀብላሏል። መከላከያ ሰራዊት የሰነዘረው ጥቃት ከባድ ስለነበር፣ ከተለያየ አቅጣጫና፣ በአየር የተደገፈ ስለነበር መቋቋም ያቃታቸው የጁንታው ምስኪን ሚሊሻና ልዩ ሃይል እጅ ለመስጠት ተገደዋል።
ነጻ በወጡት መንደሮችና አካባቢዎች መከላከያ አቀባበል ተደርጎለታል። ፋና እንዳለው የአካባቢው ነዋሪዎችምበ ፅንፈኛው የሕወሓት ቡድን ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ ጭቆናበደል ሲደርስባቸው እንደነበር ገልፀዋል።
አሁን ላይ በመከላከያ ሰራዊት፣ በአማራ ልዩ ኃይልና በሚሊሻ አባላት ከትህነግ ከሐዲ ቡድን ነጻ በመውጣታቸው ደስታቸውን እየገለጹ ነው። የትግራይ ህዝብ የዘራፊውን ትህነግ ቡድን ሐገርን የማፍረስ ተግባር በመቃወም ከመንግስት ጎን መቆም እንዳለባቸውም መናገራቸውን ሲል የአማራ ክልል ማስ ሚዲያ ዘግቧል። ከጁንታው ሃይል በኩል እስካሁን የተባለ ነገር የለም። ምን አልባትም ሰሞኑንን በቁጥጥር ስር ውላ ሰላማዊ እንቅስቃሴ በጀመረችው ሁመራ ነዋሪዎች አስተያየት እንደሰጡት ተብሎ እንደቀረበው አይነት መግለጫ ማምሻውን እንደሚቀርብ ይገመታል።
- ሰበር ዜና – ትህነግ በዲፕሎማሲ ዘመቻ ቀውስ ገጠመው፤ “ በሃሰት መረጃ አሳፈራችሁን ” የቅርብ አጋሮቻቸውበጦርነት የተመታውና ህልውና ሙሉ በሙሉ እንዳከተመለት የተነገረለት ትህነግ በዲፕሎማሲ አስደንጋጭ ቀውስ እንደገጠምው ተሰማ። ሌት ከቀን ሲሟገቱላቸው የነበሩ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች “ አዋረዳችሁን” ሲሉ ሃዘናቸውን እንደገለጹላቸው ታወቀ።Continue Reading
- መከላከያ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ “ጁንታውን” ሙሉ በሙሉ መደምሰሱን አስታወቀ! በርካታ በቁጥጥር ስር ውለዋልሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የጁንታውን ሃይል በከፍተኛ ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሙሉ በሙሉ መደምሰሱን አስታወቁ። ” ጁንታው ካሁን በኋላ ሰራዊትና ጠባቂ ይዞ መንቀሳቀስ አይችልም”Continue Reading
- Ethiopia’s transition misrepresented. Reply to Obang Metho… To set the record, Mr. Obang, my self as part of his admirers and supporters, started out his career in search of justice for hisContinue Reading
- ብርሃኑ ነጋ አቋማቸውን ቀየሩ፤ ኢዜማ ደርግ በግፍ የዘረፈውን የግል ሃብት ለተከራይ እንደሚሸጥ ይፋ አደረገ፤ የኢዜማ የ ” ፍትህ” ሩጫኢዜማ አዲስ አበባ ላይ ካሸነፈ ደርግ በግፍ የዘረፈውን የግለሰብ ንብረት በሁለት ዓመት ውስጥ እንደሚሸጥ ይፋ አደረገ። የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ነጋ ለዓመታት እንደ ፖለቲከኛም ሆነ እንደContinue Reading