የሐሰተኛ ገንዘብ ሥርጭቱ ሊጨምር እንደሚችል፤ ሕጋዊ ገንዘቡም በሕገ ወጥ መልኩ ሊዘዋወር እንደሚችል ተገምቷል፡፡ በ2012 ዓ.ም ክልሉን ለማዳካም በትኩረት የሚሠሩ አካላት በክልሉ ሃሰተኛ ብር ረጭተው ለፍትህ አካላቱ ተቸማሪ የስራ ጫና ሆኖ ነበር። ከዚ ልምድና መሰረታዊ እውነታዎች በመንሳት በውስጥ ቁጥጥርና የማስተማር ስራ፣ በድንበር ሃሰተኛ ብር እንዳይገባ ከመከለከያና የፌደራል ልዩ ሃይላት ጋር ላፍታም ሳይተኛ ቁጥጥር እንደሚያደርግ ግልጽ አድርጓል
የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ሐሰተኛ የብር ኖት ስርጭትን እና ሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመቆጣጠር አቅጣጫ ማስቀመጡን አስታወቀ፡፡
ኢትዮጵያ ነባሮቹን ባለ10፣ 50 እና 100 የብር ኖቶች መተካታቸውና አዲስ ባለ200 ብር ገንዘብ ትናንት ይፋ አድርጋለች፡፡
የብር ኖቶች ለውጥ መደረጉን ተከትሎም ከኢትዮጵያ ውጪ ያለአግባብ የተከማቸ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ወደ ሀገር ይገባል ተብሎ ይገመታል፡፡ የሐሰተኛ ገንዘብ ስርጭት ሊኖር እንደሚችልም የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
ፖሊስ ኮሚሽኑ እንደገለጸው በአማራ ክልል በተለያዩ ጊዜያት የሐሰተኛ ገንዘብ ሥርጭት ነበር፡፡ በተለይም በበዓላት ጊዜ በስፋት ይሠራጭ እንደነበር በኮሚሽኑ የማኅበረሰብ ወንጀል መከላከል መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ጀማል መኮንን ተናግረዋል፡፡ በ2012 ዓ.ም ክልሉን ለማዳካም በትኩረት የሚሠሩ አካላት ተሰማርተው እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡
ይህ የወንጀል ድርጊት ማኅበረሰቡን ለችግር መዳረጉንና ለፀጥታ ኃይሉም ተጨማሪ የሥራ ጫና እንደነበር ነው ኮማንደር ጀማል የተናገሩት፡፡ ኮማንደር ጀማል እንዳሉት የብር ኖት ለውጥ መደረጉ ለስርጭት የተዘጋጀ ሐሰተኛ የብር ኖትን ለማክሸፍ ከፍተኛ ሚና አለው፡፡
በዚህ ምክንያት የሐሰተኛ ገንዘብ ሥርጭቱ ሊጨምር እንደሚችል፤ ሕጋዊ ገንዘቡም በሕገ ወጥ መልኩ ሊዘዋወር እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የክልሉ ከፍተኛ የፖሊስ ኃላፊዎች የማኔጅመንት አባላት ዛሬ መስከረም 5/2013 ዓ.ም በጉዳዩ ላይ ውይይት አድርገው ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ የሚቻልበትን አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
በዚህ መሠረት እስከ ቀበሌ ያሉ የፀጥታ ኃይል አባላት ማኅበረሰቡ በሕገ ወጥ የገንዘብ እንቅስቃሴ እንዳይሳተፍ በማስተማር፣ በማስጠንቀቅና በመቆጣጠር ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሠሩም ታውቋል፡፡ ኮማንደር ጀማል እንደተናገሩት በሱዳን በኩል ገንዘብ እንዳይገባም የክልሉ የልዩ ኃይልና የመደበኛ ፖሊስ አባላት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት እና ከፌዴራል ፖሊስ ጋር በመሆን ጠረፍ ላይ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር ያደርጋሉ፡፡
ሐሰተኛ ገንዘብ ወደ ማኅበረሰቡ ከገባ ሕዝቡ ለኪሳራ ይጋለጣል፡፡ ሐሰተኛ ገንዘብ ይዞ የሚገኝ ግለሰብም በሕግ ተጠያቂ እንደሚሆን ነው ኮማንደር ጀማል ያስታወቁት፡፡
ማኅበረሰቡ በእጁ ያለውን ገንዘብ በሕጋዊ የገንዘብ ተቋማት በመጠቀም ሕጋዊ ገንዘቡን ከሚያሳጡ እና የተከለከሉ ነገሮችን ከማድረግ እንዲቆጠብ አሳስበዋል፡፡ ሕገ ወጥነትን በመከላከል ረገድ ሕዝቡ በተለመደው አግባብ ለፀጥታ ኃይሉ ተባባሪ እንዲሆንም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
“ሐሰተኛ የብር ኖቶችን እና ሕጋዊ የመገበያያ ገንዘብን ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ ማስቆም ወንጀልን ከመከላከል ባሻገር በሀገር ላይ የሚደርስን ምጣኔ ሀብታዊ ኪሳራ መታደግ ነው” በማለትም በየደረጃው ያሉ የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች በቆራጥነት ሕግ የማስከበር ሥራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ደጀኔ በቀለ
- Israeli ‘sex tourism’ is the fruit of normalisation with the UAEIt is hard to believe the testimonies of Israeli tourists returning from the UAE, in which they describe Dubai as the Las Vegas of theContinue Reading
- UAE diplomatic delegation intervenes to reactivate Renaissance Dam negotiationsThe official Sudan News Agency (SUNA) announced on Wednesday that a delegation from the United Arab Emirates (UAE) Ministry of Foreign Affairs concluded a one-day visitContinue Reading
- Egypt invetors in Ethiopia request compensation for losses due to Tigray conflictBy Shaimaa Al-Aees Egyptian investors in Ethiopia’s Tigray region are awaiting the federal government’s response to the former’s requests of compensations for production halt and lossesContinue Reading
- “ትህነግ መጀመሪያ ቃል ነበር – ማሌሊትን ለብሶ በእኛ አደረ “እስኪ መለስ ይቀስቀሱ። እስኪ መለስ ፊት ብዙ የድምጽ መቅጃ ይደርደር። ድምጸ ወያኔ ይጠይቅ። ሁሉም ባይሰማ የትግራይ ሕዝብ፣ ከትግራይ ሕዝብም በተለይም ” አምላክ ትግራይን ፈጠረ፣ ትግራይምContinue Reading