በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ በቁጥጥር ስር ዋለ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አብዱልአዚም መሀመድ እንደገለጹት በክልሉ በሚገኙ 4 የተለያዩ ኬላዎች በተደረገ ፍተሻ 2 ሚሊዮን 370 ሺህ ብር በቁጥጥር ስር የዋለው።
በክልሉ ኩርሙክ ወረዳ ሱዳን ድንበር አካባቢ በግለሰብ ሲዘዋወር የነበረ 600 ሺህ ብር የሚሆን ገንዘብ በቁጥጥር ስር እንደዋለ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡ በመተከል ዞን ጉባ ወረዳ ማንኩሽ ኬላም 300 ሺህ ብር ፣በአሶሳ ከተማ አሶሳ ኬላ ደግሞ 700 ሺህ ብር በቁጥጥር ስር ውሏል ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ በአሶሳ ዞን ቡልድግሉ ወረዳ ጎንቆሮ ኬላ ደግሞ 770 ሺህ ብር በቁጥጥር ስር መዋሉንም ኮሚሽነሩ አመልክተዋል፡፡
የክልሉ መንግስት መሠል ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመቆጣጠር ክትትሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹት ኮሚሽነር አብዱልአዚም ኅብረተሰቡ አስፈላጊውን ትብብር ማድረጉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
- ትህነግ – ሚስጥሩ “ሚስጥር” የሆነበት ተዋጊ!! የፕላኔቱ ሆቴል ሚስጢር ዜሮ ብዜት!!ኢትዮ 12 ዜና – “ ሚስጢር ነበር” ይላል የኢትዮ 12 መረጃ አቀባይ። ሚስጥሩ በሚስጢር የተቆለፈ መሆኑንን የማያውቁ ሚስጢረኞች ሲል ተንደርድሮ ፓርላማ ይገባል። ፓርላማ ገብቶ ከትንታኔውContinue Reading
- Ethiopia Briefs EU Delegation On Latest Development In TigrayMinister of Finance Ahmed Shide received Erik Habers, Charge De Affair and Head of Cooperation of EU Delegation in Addis Ababa at his office today.Continue Reading
- እጃቸውን የሰጡ ከፍተኛ መኮንኖች ተገደው ሚኒሻ ሲያደራጁ እንደነበር ለችሎት አስረዱበቅርቡ ለአገር መከላከያ ሠራዊት እጃቸውን የሰጡት ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ኒሻን ጨምሮ አራት የቀድሞ የጦር መኮንኖች በህወሓት ጸረ ሰላም ቡድን አመራሮች ተገደው ሚኒሻዎችን ሲያደራጁ እንደነበር ለፍርድContinue Reading
- ምርጫ ቦርድ ኢዜማን ጨምሮ ስድስት ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ቀይሩ አለ፤ ኢዜማ በመላው አገሪቱ ብቻውን እንደሚወዳደር አስታወቀስድስት የፖለቲካ ፓርቲዎች የመረጧቸውን ምልክቶች በተለያዩ ምክንያቶች ቀይረው እንዲያቀርቡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥሪ አደረገ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የፓርቲዎች የምርጫContinue Reading