ቀደም ባሉት ዓመታት መጠኑ ይህን ያህል ባይሆንም ከሰበታ አንድ የመሬት ምሪት ሃላፊ መሐንዲስ መኖሪያ ቤት ሮቶ የውሃ ጋን ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው ብር ተይዞ ነበር። ከዚያ ግዜ በሁዋላ ገንዘብ አልጋ ስር ተቀብሮ ሲገኝ በብዛትም በዓይነትም ይህ ትልቁ ነው።
ባሌስትራ ወርቅ ነው በማለት በቅንጅት ብሄራዊ ባንክን ሲዘርፉ የነበሩ ከበርካታ ጩኸት በሁዋላ ዋናዎቹ ጠግበው ከኮበለሉ በሁዋላ በቁጥጥር ስር የዋሉት ዱርዬ ሃብታሞች ቤት ሲፈተሽ ብር የተገኘው እመኝታ ስር በተሰራ የአርማታ ጉድጓድ ውስጥ ነበር። አንደኛው ተጠርጣሪ በአርማታ እተሰራው ጉድጓድ ላይ ዘመናዊ ማድራስ አድርጎ ለእናቱ ከላይ ያስተኛ ነበር። ይህ ዜና በውቅቱ አስገራሚ ነበር።
ዛሬ ከሰበታ የተሰማው ሌላ ዜና ደግሞ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ብሮች አልጋ ስር ተከማሽቶ መገነቱ ነው። የተገኘው ደግሞ አንድ ፓኪስታናዊ ተከራይቶ በሚኖርበት የመኖሪያ ቤት ውስጥ ነው። ፋና የከተማውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቀነኒሳ ዳዲ ጠቅሶ እንደዘገበው ከ3 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር በላይ የእገር ውስጥ ብርና የውጭ ሀገራት ገንዘቦች በተጠቀሰው ሰው ቤት ተከማችቶ ተይዟል።
ከተማው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቀነኒሳ ዳዲ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት የተያዘው ገንዘብ 3 ሚሊየን 751 ሺህ 830 የኢትዮጵያ ብር፣ 2 ሺህ 950 የአሜሪካ ዶላር እና የዱባይ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬት፣ የፓኪስታንና የኦማን ገንዘቦች ናቸው፡፡
በከተማው የ3ኛ ክፍለ ከተማ የፖሊስ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ታደሰ ሁሪሳ ገንዘቡ በግለሰብ ቤት ውስጥ አልጋ ስር ተከማችቶ የተያዘው በህብረተሰቡ ጥቆማና በፀጥታ መዋቅር ክትትል ነው ብለዋል፡፡ገንዘቡ የተያዘው አንድ ፓኪስታናዊ ተከራይቶ በሚኖርበት የመኖሪያ ቤት ውስጥ ነውም ብለዋል ኃላፊው፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ወደ ፊትም ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርና ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን ለመቆጣጠር በትኩረት የሚሰራ መሆኑን አቶ ቀነኒሳ ዳዲ ተናግረዋል፡፡
- ትህነግ – ሚስጥሩ “ሚስጥር” የሆነበት ተዋጊ!! የፕላኔቱ ሆቴል ሚስጢር ዜሮ ብዜት!!ኢትዮ 12 ዜና – “ ሚስጢር ነበር” ይላል የኢትዮ 12 መረጃ አቀባይ። ሚስጥሩ በሚስጢር የተቆለፈ መሆኑንን የማያውቁ ሚስጢረኞች ሲል ተንደርድሮ ፓርላማ ይገባል። ፓርላማ ገብቶ ከትንታኔውContinue Reading
- Ethiopia Briefs EU Delegation On Latest Development In TigrayMinister of Finance Ahmed Shide received Erik Habers, Charge De Affair and Head of Cooperation of EU Delegation in Addis Ababa at his office today.Continue Reading
- እጃቸውን የሰጡ ከፍተኛ መኮንኖች ተገደው ሚኒሻ ሲያደራጁ እንደነበር ለችሎት አስረዱበቅርቡ ለአገር መከላከያ ሠራዊት እጃቸውን የሰጡት ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ኒሻን ጨምሮ አራት የቀድሞ የጦር መኮንኖች በህወሓት ጸረ ሰላም ቡድን አመራሮች ተገደው ሚኒሻዎችን ሲያደራጁ እንደነበር ለፍርድContinue Reading
- ምርጫ ቦርድ ኢዜማን ጨምሮ ስድስት ፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ቀይሩ አለ፤ ኢዜማ በመላው አገሪቱ ብቻውን እንደሚወዳደር አስታወቀስድስት የፖለቲካ ፓርቲዎች የመረጧቸውን ምልክቶች በተለያዩ ምክንያቶች ቀይረው እንዲያቀርቡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥሪ አደረገ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የፓርቲዎች የምርጫContinue Reading