የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ በኢትዮጵያ አዲሱ የብር ለውጥ ከተጀመረ ወዲህ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ገንዘብ ወደ ባንክ ስርዓቱ መመለሱንና 580 ሺህ ዜጎች አዲስ የባንክ የሂሳብ መክፈታቸውን አስታወቁ።
አዲሱ የብር ለውጥ ከተጀመረ ባሉት 14 ቀናት ውስጥ ብቻ 580 ሺህ ዜጎች አዲስ የሂሳብ አካውንት መክፈታቸውን ትፋ ያደረጉት አቶ ይናገር፣ ከባንክ ስርዓት ውጭ ከሚንቀሳቀሰው ሃብት ውስጥ 14 ቢሊዮን ብር ወደ ባንክ ስርዓት መግባቱን አመልክተዋል።
67 ቢሊየን አዲሱን የብር ኖት በመላ አገሪቱ ባሉ 99 ነጥብ 9 በመቶ የባንክ ቅርንጫፎች ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲደረስ መደረጉን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ተናግረዋልልል
የብር ለውጡ ያስፈለገበት አንዱ ዓላማ ከባንክ ውጭ ያለን ገንዘብ ወደባንክ የማስመለስ ጉዳይ እንደነበር ያስታወሱት የባንኩ ገዥ ÷ ከዚህ አንጻር በአጭር ጊዜ ውስጥ ይሄንን ያህል ገንዘብ ወደ ባንክ ስርዓቱ መመለሱ የዓላማውን መሳካት ያሳያል ብለዋል።
የብር ለውጡ ሌላኛው ዓለማ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን ማሳደግ እንደሆነ የገለጹት ዶክተር ይናገር÷ አዲስ የባንክ ሂሳብ ከተከፈቱት 580 ሺህ ዜጎች በተጨማሪ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች አካውንት ይከፍታሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ህብረተሰቡ በተያዘው የጊዜ ገደብ ውስጥ በእጁ ያለውን አሮጌ የብር ኖት በአዲሱ መቀየር እንዳለበትም ዶክተር ይናገር ማሳሰባቸውን ኢቢሲ ነው የዘገበው።
- የአምነስቲ ” ሽንቁረ ብዙ” ሪፖርት የተከፋዮች የቲውተር ዜና ድምርአገር መከላከያ ባላሳበው መንገድ ተጨፍጭፏል። በመኪና ተጨፍልቋል። እንደጠላት ” ሌባ ” እየተባ ባዶ እግሩን መሳሪያ ተወድሮበት ተተፍቶበታል፤ ብወልቃይት ጠገዴ፣ በራያ የሚኖሩ ሰዎች ላይ የተፈጸመው ግፍ፣Continue Reading
- Ministry Urges Amnesty Int’l to Use Appropriate Sources in Report to Uncover the TruthAmnesty International should use appropriate sources in its report to uncover the truth regarding allegations related to the incidents in the city of Axum, accordingContinue Reading
- Ethiopia: Eritrean troops’ massacre of hundreds of Axum civilians may amount to crime against humanityAmnesty International interviewed 41 survivors and witnesses to mass killings in November Troops carried out extrajudicial executions, indiscriminate shelling and widespread looting Satellite imagery analysisContinue Reading
- በትግራይ 3.5 ሚሊዮን ተረጂዎች የዕለት ቀለብና ተመሳሳይ እርዳታ እየተደረገላቸው ነውበትግራይ ለ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች የዕለት ደራሽ ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎች እየተደረገ መሆኑን የብሄራዊ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በክልሉ በነበረው ህግ ማስከበርContinue Reading