ማህበራዊ ድረ-ገጽን በአግባቡ አለመጠቀም የህግ ተጠያቂነትን እንደሚያስከትል ተገለጸ፡፡ ቅጣቱ በህግ በተደነገገው መሰረት እስከ መቶ ሺህ ብርና አምስት ዓመት የሚደርስ ቅጣት እንደሚያስቀጣ ተገለጸ።
በሀገራችን ከማህበራዊ ድረ-ገጽ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ ክፍተቶች እንደሚስተዋሉ በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ህግ የሰውዘር አበበ ናቸው የገለጹት።
የማህበራዊ ድረ-ገጽ አጠቃቀምን በማዘመንና በህግ በተቀመጠው አግባብ በመጠቀም እራስን ከተጠያቂነት መከላከል እንደሚገባ የገለጹት ዐቃቤ ህጓ የማህበራዊ ድረ-ገጽ አጠቃቀምን አስመልክቶ በህግ የተቀመጡ ገደቦችን ሳያልፉ ለታለመለት አላማ ብቻ በመጠቀም ተገቢ ነው ብለዋል፡፡
ነገር ግን የማህበራዊ ድረ-ገጽን ላልተፈለገ እኩይ ተግባር በማዋል የሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግ ለማስተላለፊያነት በመጠቀም የሌሎችን ሰብዓዊ ክብር የሚነኩ እንዲሁም ባልተጨበጠ መረጃ ህብረተሰቡ ግራ እንዲጋባ ለማድረግ ያለአግባብ በሚጠቀሙ አካላትን ተጠያቂ የሚያደርግ የሀሰሰኛ መረጃ ስርጭትና የጥላቻ ንግግን የሚከለክል አዋጅ ወጥቶ ስራ ላይ እንደዋለ አስታውሰዋል፡፡
በአዋጁ ከተካተቱት መካከልም የጥላቻ ንግግርን በብሮድካስት፣ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያ ወይንም ሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎችን በመጠቀም ያስተላለፈ እስከ 2 አመት በሚደርስ እስራትና በብር 100,000 እንደሚያስቀጣ አብራርተዋል፡፡
በተጨማሪም በተላለፈው የጥላቻ ንግግር ምክንያት በግለሰብ ወይም በቡድን ላይ ጥቃት ደርሶ እንደሆነ የቅጣቱ ጊዜ እስከ 5 ዓመት የሚደርስ ሲሆን ሀሰተኛ መረጃዎችን በአደባባይ ስብሰባዎች፣ በብሮድካስት፣ በማህበራዊ ሚዲያ ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በምስል፣ በጽሁፍ ወይም በቪዲዮ በመጠቀም ያሰራጨ እንደሆነ 1 ዓመት በሚደርስ እስራት ወይም በ50,000 ብር ቅጣት ሊተላለፍበት ይችላል ያሉት ዐቃቤ ህጓ መረጃው ከ5000 በላይ ተከታይ ባለው ማህበራዊ ድረ-ገጽ የተላለፈና ጉዳት የደረሰ እንደሆነ ግን የቅጣት መጠኑ ከ2 እስከ 5 ዓመት ሊደርስ ይችላል ብለዋል፡፡
ምንጭ – አቃቤ ህግ
- እጃቸውን የሰጡ ከፍተኛ መኮንኖች ተገደው ሚኒሻ ሲያደራጁ እንደነበር ለችሎት አስረዱበቅርቡ ለአገር መከላከያ ሠራዊት እጃቸውን የሰጡት ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ኒሻን ጨምሮ አራት የቀድሞ የጦር መኮንኖች በህወሓት ጸረ ሰላም ቡድን አመራሮች ተገደው ሚኒሻዎችን ሲያደራጁ እንደነበር ለፍርድContinue Reading
- እነ ጃዋር ” በዛሬው ቀጠሮ የእምነት ክህደት ቃል ለመስጠት ዝግጁ አይደለንም” ሲሉ የመማከሪያ ጊዜ ጠየቁበተሻሻለው ክስ መሰረት የእምነት ክህደት ቃል እንዲሰጥ ጥያቄ የቀረበላቸው እነ ጃዋር መሐመድና አስራ ስምንት ተጠርጣሪዎች ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው በጠየቁት መሰረት ፍርድ ቤት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። ጠበቆቻቸው Continue Reading
- በሙስና ወንጀል የተገኘን ንብረት ማሳገድ ፤ ማስመለስ፡ ማስወረስ እና ማካካስ በፀረ ሙስና ህጎች. በሙስና የተገኘን ሀብት ማገድ፤ ማስመለስ እና የማካካሻ ምንነት በዓለም ዐቀፍ ደረጃ የተመዘበረ ሀብት ማስመለስ ጽንሰ ሀሳብ መነሻ በሙስና ወንጀል፤ በታክስ ማጭበርበር ፤ በህገ ወጥContinue Reading
- ህገወጥ ሰው አዘዋዋሪ ወንጀለኞችን ለመመርመርና ማስቀጣት የሚያስችል አዲስ የሰነድ ርክክብ ተደረገበሰዎች የመነገድና ሰዎችን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀሎችን ለመመርመርና ለማስቀጣት የሚያስችል ወጥ የአሰራር ስርአት ተዘርግቶ የሰነድ ርክክብ ተካሄደ ጥር 14/2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሚፈፀሙ በሰዎችContinue Reading