ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ ክስ የቀረበባቸው ተከሳሾች የክስ መቃወሚያ የሌላቸው መሆኑን ለፍርድ ቤት ገልፀዋል
በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ዙርያ ክስ የቀረበባቸው 1ኛ ጥላሁን ያሚ፣ 2ኛ ከበደ ገመቹ፣ 3ኛ አብዲ አለማየሁ፣ እና 4ኛ ላምሮት ከማል፤ ዛሬ ጥቅምት 04/2013 ዓ.ም ለነበራቸው ቀጠሮ ያላቸውን የክስ መቃወሚያ ይዘው እንዲቀርቡ በተሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ቀርበው ቀድሞ በነበራቸው ቀጠሮ ላይ ሶስቱ ተከሳሾች አቅም ስለሌለን መንግስት ጠበቃ ያቁምልን በማለት ጠይቀው የነበረ ሲሆን፤ 4ኛ ተከሳሽ ደግሞ ጠበቃ በግሌ የመቅጠር አቅሙ ቢኖረኝም ፍቃደኛ ሆኖ ጥብቅና የሚቆምልኝ ሰው ማግኘት ባለመቻሌ ጠበቃ ይመደብልኝ በማለት ጠይቀው የነበረ በመሆኑ በመንግስት ጠበቃ ተመድቦላቸው ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡
የተከሳሾቹ ጠበቃ በበኩላቸው፤ 4ኛ ተከሳሽ ላምሮት ከማል ጠበቃ በግል የመቅጠር አቅም እያላቸው ከህግም አንፃር ተገቢ ባለመሆኑ መንግስት በነፃ ጠበቃ ሊያቆምላቸው አይገባም በሚል ቅሬታቸውን አቅርበው፤ ፍርድ ቤቱም በበኩሉ ትዕዛዙ የተሰጠው ህጎችን ከግንዛቤ በማስገባት በመሆኑ ፍትህ እንዳይጓደል ትዕዛዙ በነበረው መሰረት እንዲቆይ በማለት ለጠበቃው ምላሽ በመስጠት ችሎቱ እንዲቀጥል አድርጓል፡፡
ችሎቱ ቀጥሎም ተከሳሾቹ ዛሬ በነበራቸው ቀጠሮ መሰረት በተመደበላቸው ጠበቃ አማካኝነት በቀረበባቸው ክስ ላይ ምንም የክስ መቃወሚያ የሌላቸው መሆኑን ለፍርድ ቤቱ ገልፀዋል፡፡
በመቀጠልም የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ ተጠይቀው እያንዳንዳቸው ተከሳሾች በክሳቸው ላይ የተጠቀሰውን ወንጀል አልፈፀምኩም በማለት ቃላቸውን ለፍርድ ቤቱ ሰጥተዋል፡፡
ፍርድ ቤቱም የተከሳሾችን ምላሽ ካዳመጠ በኋላ የዐቃቤ ህግን ምስክሮች ቃል ለመስማት ለህዳር 23, 24 እና 25 ቀጠሮ በመስጠት የእለቱ ችሎት ተጠናቋል፡፡
ምንጭ ጠቅላይ አቃቤ ህግ
- በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በተጠርጠሩ አራት ተከሳሾች ብይን ሰጠየፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የፀረ-ሽብርና ሕገ መንግሥት ጉዳዮች ወንጀል ምርመራ ችሎት በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ተጠርጥራ የነበረውን ላምሮት ከማልን በነጻ አሰናበተ። የተቀሩትን ሦስቱንContinue Reading
- በእነ ጃዋር የህክምና ጥያቄ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሁሉንም ተከራካሪዎች ጥያቄ ውድቅ አደረገ፤ ቃሊቲ ሆነው ይታከማሉ፤በእነ ጃዋር ጉዳይ ይግባኝ የቀረበለት የየቅላይ ፍርድ ቤት የክፍተኛውን ፍርድቤትና የአቃቤ ህግ ይግባኝ ውድቅ አድርጎ አዲስ ውሳኔ አሳለፈ። የፌደራል ማረሚያ ቢት ምክትል አስተዳዳሪ ታስረርው እንዲቀርቡContinue Reading
- የሙለር ሪል ስቴት ባለቤት አቶ ሙሉጌታ ተስፋኪሮስ በሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸውየሙለር ሪል ስቴት ባለቤት አቶ ሙሉጌታ ተስፋኪሮስ በሙስና ወንጀል ዐቃቤ ህግ ክስ መሰረተባቸው፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በዛሬው እለት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮContinue Reading
- ከህዋሓት አመራሮች የጥፋት ተልዕኮ ተቀብሎ ጥቃት ለማድረስ ተንቀሳቅሷል የተባለ ተጠርጣሪ ላይ ክስ ሊመሰረት ነውከህዋሓት አመራሮች የጥፋት ተልዕኮ ተቀብሎ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ህዝብ ላይ ጥቃት ለማድረስ ተንቀሳቅሷል የተባለ ተጠርጣሪ ላይ ክስ ሊመሰረት ነው ከህዋሓት አመራሮች የጥፋት ተልዕኮ ተቀብሎ በአዲስContinue Reading