ለጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በተጠራ የድጋፍ ሰልፍ ላይ በተቀነባበረ ትስስር ቦንብ ወርውረው ጉዳት ያደረሱ ተከሳሾች ላይ ከ5 እስከ እድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንደተፈረደባቸው ተገለጸ።
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በኦፊሳል ገጹ ይፋ እንዳደረገው ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተጠራው የድጋፍ ሰልፍ ላይ በመስቀል አደባይይ ቦንብ በመወርወር ለሁለት ሰዎች ህይወት ማለፍ እና ለ150 ሰዎች የአካል ጉዳት መድረስ ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ 5 ግለሰቦች ከ5 ዓመት እስከ እድሜ ልክ ፅኑ እስራት ቅጣት እንደተወሰነባቸው ይፋ አድርጓል።
በዚሁ መሰረት 1ኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ በ23 ዓመት፣ 2ኛ ተከሳሽ ብርሀኑ ጃፈር 22 ዓመት፣ 3ኛ ተከሳሽ ጥላሁን ጌታቸው በእድሜ ልክ፣ 4ኛ ተከሳሽ ባህሩ ቶላ በ17 ዓመት እንዲሁም 5ኛ ተከሳሽ ደሳለኝ ተስፋዬ በ5 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ የህገ መንግስት እና የፀረ ሽብር ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ብይን መስጠቱ ታውቋል።
- በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በተጠርጠሩ አራት ተከሳሾች ብይን ሰጠየፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የፀረ-ሽብርና ሕገ መንግሥት ጉዳዮች ወንጀል ምርመራ ችሎት በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ተጠርጥራ የነበረውን ላምሮት ከማልን በነጻ አሰናበተ። የተቀሩትን ሦስቱንContinue Reading
- በእነ ጃዋር የህክምና ጥያቄ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሁሉንም ተከራካሪዎች ጥያቄ ውድቅ አደረገ፤ ቃሊቲ ሆነው ይታከማሉ፤በእነ ጃዋር ጉዳይ ይግባኝ የቀረበለት የየቅላይ ፍርድ ቤት የክፍተኛውን ፍርድቤትና የአቃቤ ህግ ይግባኝ ውድቅ አድርጎ አዲስ ውሳኔ አሳለፈ። የፌደራል ማረሚያ ቢት ምክትል አስተዳዳሪ ታስረርው እንዲቀርቡContinue Reading
- የሙለር ሪል ስቴት ባለቤት አቶ ሙሉጌታ ተስፋኪሮስ በሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸውየሙለር ሪል ስቴት ባለቤት አቶ ሙሉጌታ ተስፋኪሮስ በሙስና ወንጀል ዐቃቤ ህግ ክስ መሰረተባቸው፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በዛሬው እለት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮContinue Reading
- ከህዋሓት አመራሮች የጥፋት ተልዕኮ ተቀብሎ ጥቃት ለማድረስ ተንቀሳቅሷል የተባለ ተጠርጣሪ ላይ ክስ ሊመሰረት ነውከህዋሓት አመራሮች የጥፋት ተልዕኮ ተቀብሎ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ህዝብ ላይ ጥቃት ለማድረስ ተንቀሳቅሷል የተባለ ተጠርጣሪ ላይ ክስ ሊመሰረት ነው ከህዋሓት አመራሮች የጥፋት ተልዕኮ ተቀብሎ በአዲስContinue Reading
- ፖሊስ አባይ ወልዱ ቀሚስ ለብሰው መያዛቸውን፣ከባንክ ገንዘባን ወርቅ ተዘርፎ እንዲታደል መደረጉን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስረዳ– የእነስብሀት ነጋ ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል። ተጠርጣሪዎቹ በፌፌራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ነው ጉዳያቸው የታየው ፡፡Continue Reading