የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ጌታቸው ረዳ በዛሬው እለት ሪፖርተር ጋዜጣ የአውሮፓ መቀሌ በመሄድ ድርድር ማድረጋቸውን የዘገበው ስህተት መሆኑንን አስታወቁ። ሰዎችሁ መቀሌ ሂደዋል መባሉም ሃሰት ነው አሉ። ዜናውን ማስተባበል የተፈለገው የህብረቱ የአዲስ አበባ ሰዎች ማስተባበያ እንደሚያወጡ በመሰማቱ እንደሆነ ዛጎል ሰምቷል።
አቶ ጌታቸው በግል የቲዊተር ገጻቸው ይፋ እንዳደረጉት የአውሮፓ ልዑክ ወደ መቀሌ አላመራም። ሪፖርተር እሳቸው ጠቅሶ ከልዑክ ቡድኑ ጋር በአካል ወይይት ተደርገ በሚል የተዘገበውን ዜና ” እጅግ አሳሳች” ሲሉ የገለጹት አቶ ጌታቸው ቃል በቃል ” በቅርቡ ምንም የአውሮፓ ልዑክ ወደ ትግራይ አልመጣም” ብለዋል።
ለህብረቱ ምክትል ሃላፊ ስለ ህወሃት አቋም ማስረዳታቸውን፣ ይህንንም ያደረጉት በዘመኑ ቴክኖሎጂ እንጂ በአካል አለመሆኑንን አቶ ጌታቸው ይፋ አድርገዋል። ስለውጤቱም ሆነ ስለ ተደረገው ውይይት፣ መቼ ወይም ከምን ያህል ወር በፊት በስም ላልጠቀሷቸው ሃላፊ ማብራሪያ እንደሰጡ ግን ይፋ አላደረጉም።
አቶ ጌታቸው ይህንን ቢሉም ዜናውን ያተመው ሪፖርተርም ሆነ ከሪፖርተር ዜናውን ወሰደው ያሰራጩና ያነበቡ ሚዲያዎች ማስተባበያ ስለማውጣታቸው ይህ እስከታተመ ድረስ አልታወቀም። አቶ ጌታቸው ዜናውን ባያርሙትም አውሮፓ ህብረትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ ሊያወጡ እንደሚችሉ ግምት ነበር። ይሁን እንጂ ዛጎል አቶ ጌታቸው ጋዜጣውን ሳይጠብቁ እርምት ያሰራጩት ይህንኑ ስመተው ነው። ሪፖርተር በፊት ለፊት ገጹ ዜናውን ማተሙ ይፋ እንደሆነ በሶሻል ሚዲያዎች የዜናው ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኖ ውሎ ነበር፤
- እውነትን ለሥልጣን መናገር !! ሳማንታ ፖወር – ለኢትዮጵያ ዘር ፖለቲከኞች መከላከል አቁሚ!እ.ኤ.አ. በሚያዝያ ወር መጨረሻ ላይ በሪቻርድ ክላርክ ስር የሰራችው በNSC መረጃ ክፍል ውስጥ ስትሰራ የነበረችው ሱዛን ራይስ ፣ “የዘር ማጥፋት ወንጀል” የሚለውን ቃል የምንጠቀም ከሆነContinue Reading
- Speaking Truth to Power, Samantha: Stop Defending Ethiopia’s “Proud Boys”!Samantha Power unleashed by Susan Rice to defend accused insurrectionists on trial in Ethiopia as “opposition leaders” In “Julius Caesar”, Shakespeare’s Mark Antony, the loyalContinue Reading
- US Attempt To Make Pronouncements On Ethiopia’s Internal Affairs Regrettable :MoFAThe Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia (MoFA) has rejected the press statement issued by the US Secretary of State Mr. Antony J. Blinken yesterdayContinue Reading
- “አማራ ከትግራይ ክልል ውጣ”አሜሪካ ”ግፍ” ታውቃለች? ጋምቤላ፣ ማይካድራ፣ ራያ፣ በደኖ፣ሆራ፣ ዋተር…ምን ተደርጓል?አሜሪካ እጅግ አስገራሚ መግለጫ አሰራጭታለች። አማራ ከትግራይ ክልል ይውጣ ብላለች። በትግራይ ግፍ መፈጸሙን አምናለች። ግን ለሜሪካ ” ግፍ” ምንድን ነው? አሜሪካኖች ስለ ግፍ የማውራት ሞራልContinue Reading