የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በምዕራብ ወለጋ ዞን በተፈጸመው ጥቃት ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር ሰላሳ ሁለት እንደሆኑ፣ ጥቃቱን የመራውና ያቀነባበረው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር እያለ ራሱን የሚጠራው ቡድን ከኦነግ ሸኔ ጋር እንደፈጸሙት ተገለጸ። ከድርጊቱ ፈፃሚዎች የተወሰኑት መያዛቸው ታውቋል።
በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ቃንቃ ቀበሌ በተፈጸመው ጥቃት ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር ሰላሳ ሁለት እንደሆነ የገለጹት
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ ናቸው። ኮሚሽነሩ ዛሬ ማምሻውን ለኢቢሲ እንዳሉት፤ በጥቃቱ የተነሳ የተፈናቀሉ 200 ያህል አባወራዎችን ናቸው።
የዞኑ አስተዳደር ለአማራ ቲሌቪዥን እንዳሉት ጥቃት አድራሺዎቹ ከብት በመጠበቅና እርሻቸው ላይ የነበሩ ሰላማዊ ሰዎችን ስብሰባ ጠርተው ጥድ ዛፍ ስር ከሰበሰቡ በሁዋላ ነው የገደሏቸው። ግድያው እጅግ ዘግናኝ ሲሆን ሕዝብ እንዲያየው ቀረጻው ሲጠናቀቅ አየር ላይ እንዲውል እንደሚላክ አስታውቀዋል።
መኖሪያ ቢቶችን፣ የሰብል መጠበቂያ ማማዎችን፣ በጎተራ ያለ እህል በእሳት ያጋዩት ወንበዴዎች 800 የሚሆኑ ክብቶችና ክብቶቹን እንዲነዱ አስር የሚጠጉ ሰዎችን አግተው መውሰዳቸውን አስተዳዳሪው አመልክተዋል።
በተፈጸመው ጥቃት 23 ወንድና 9 ሴቶች በድምሩ 32 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የገለጹት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፤ 10 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና እየተከታተሉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
በጥቃቱ የመኖሪያ ቤቶችና አንድ ትምህርት ቤት እንደተቃጠለ ተናግረው፤ ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር በመተባበር መልሶ የማቋቋም ስራ መጀመሩን ገልጸዋል።
የጥቃት ድርጊቱን የፈጸመው አካል ኦነግ ሸኔ መሆኑን ገልጸው፤ ከጀርባ በመሆን የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) እየደገፈው እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በተለይም ቡድኑ የታጠቃቸው እንደ ስናይፐርና ብሬል ያሉ የጦር መሳሪያዎች ህወሃት ያስታጠቀው እንደሆነ ገልጸዋል። ከኦነግ ጀርባ በመሆን ህወሃት በህብረተሰቡ ላይ ጥፋት እያደረሰ እንደሆነም ገልጸዋል።
ጥቃት የተፈጸመበት ቀበሌ ከወረዳ ከተማ በ75 ኪሎ ሜትር የሚርቅ መሆኑን ገልጸው፤ ህወሃት በብሔሮች መካከል ግጭት ለመፍጠር በስሌት የፈጸመው ተግባር ስለመሆኑ ማረጋገጫ መኖሩን ተናግረዋል። ትህነግ ይህ ከሆነ በሁዋላ አስቀድሞ ለክልሉ ህዝብ ራስህን አዘጋጅ የሚል ጥሪ በዶክተር ደብረጽዮን አማካይነት ተላልፏል።
ከድርጊቱ ፈጻሚዎች መካከል የተወሰኑት መያዛቸውን ያመለከቱት ኮሚሽነር ጀነራሉ ቀሪዎቹን ለመያዝ አሰሳው ቀጥሎ እንደሚገኝ ገልጸው፤ ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይፈጸም ከህብረተሰቡ ጋር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የመከላከያ ሰራዊት፣ የኦሮሚያ ልዩ ሃይልና የፌደራል ፖሊስ በሶስት አቅጣጫ ከበባ አድረገው ወንበዴዎቹን እያሰሱ መሆኑንን መንግስት አስታውቋል።
የአማራ ክልል፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ የኦሮሚያ ክልልና ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ” ይህንን ተጋባር ከሚፈጽምና ከሚያስፈጽም ቡድን ጋር በዚህ መልኩ መቀጠል ስለማይቻል በቃ ሊባል ይገባል” ለሚለው የህዝብ ጥያቄ መልስ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን የሚያመላክት መግለጫ በየፊናቸው አውጥተዋል።
- “የማንሸነፈው የተለየ መሣሪያ ስለታጠቅን ነው!” ሻምበል ፈይሳ ናኔቻበውጭ ወራሪም ሆነ በውስጥ ባንዳ ተባባሪ ያልተሞከረብን የለም። በየዘመናቱ እንቁ የኢትዮጵያ ልጆችን ገብረናል ፣ ቆስለናል ፣ ደምተናል ፣ ሞተናል። እኛ ኢትዮጵያዊያን እኮ ተፈትነን እንጂ ወድቀንContinue Reading
- የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጠና – ለኢትዮጵያ የሚፈጥራቸው እድሎችና ተግዳሮቶችአስተያየት – በጥላሁን እምሩ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 2018 ሩዋንዳ ኪጋሊ ላይ ተፈርሞ 2021 መባቻ ላይ ወደ ተግባር የገባው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ታቃፊ ባደረጋቸውContinue Reading
- በኢትዮጵያ ከፍተኛ መረጃ የመሸከም አቅም ያላቸው ማዕከላት ሊገነቡ ነውአዲስ አበባ በሚገኘው አይሲቲ ፓርክ ውስጥ ከፍተኛ መረጃ የመሸከም አቅም ያላቸው የመረጃ ማዕከላት (ዳታ ሴንተር) ሊገነቡ ነው፡፡ ዊንጉ አፍሪካ በተሰኘ ድርጅት የሚገነቡት እነዚህ የመረጃ ማዕከላትContinue Reading
- ኢትዮጵያ የአሰብን ወደብ በዶላር ሳይሆን በብር የኪራይ ውል የምትጠቀምበት ስምምነት ጫፍ እየደረሰ ነውኢትዮጵያና ኤርትራ በመካከላቸው የነበራቸውን “የጸብ ግድግዳ” ካፈረሱ በሁዋላ በርካታ የንግድና የጋራ ልማት ስምምነቶችን ለማድረግ እየሰሩ መሆናቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሮቹ በሁለቱም ወገን ሲጠቅሱ ማቆየታቸው ይታወሳል። የዛጎልContinue Reading